በራያ ዩኒቨርሲቲ እየተሰሩ የሚገኙ የምርምር ፕሮጀክቶች ተጠናክረው መቀጠል እንዳለባቸው ተገለጸ

በራ ያ ዩኒቨርሲቲ በ2017 ዓ.ም እየተሰሩ ያሉ የምርምር ፕሮጀክቶች የተከናወኑ ስራዎች፣ ያጋጠሙ ያሉ ችግሮች፣ የተወሰዱ መፍትሔዎች እና ለቀጣይ የሚሰሩ ስራዎች ሪፖርት (Progress Report) በዩኒቨርሲቲው የሰኔት መሰብሰቢያ አዳራሽ ሚያዝያ 02/ 2017 ዓ.ም በሚመለከታቸው ባለሙያዎች በዝርዝር ቀርበው ሀሳብ አስተያየት ተሰጥቶባቸዋል።
የዩኒቨርሲቲው ፕረዚደንት ታደሰ ደጀኔ (ፕሮፌሰር) በመርሃ ግብሩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልእክት በዩኒቨርሲቲው እየተሰሩ ያሉ የምርምር ፕሮጀክቶች ውጤታማ በማድረግ ተጨባጭ ለውጥ የሚያመጡ እና የማህበረሰቡን ችግር ፈቺ ሊሆኑ ይገባል ብለዋል።
*********//********
ራያ ዩኒቨርሲቲ ፤ ሚያዝያ 03/ 2017 ዓ.ም
ዕውቀት ለማኅበረሠባዊ ለውጥ!
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አሥፈጻሚ
********//********