ራያ ዩኒቨርሲቲ ለፍሬምናጦስ የአረጋውያን፣ ህፃናት እና አእምሮ ህሙማን እንክብካቤ ማእከል ዛሬ ነሐሴ 06 ቀን 2017 ዓ.ም ከ1.2 ሚልዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው ቁሳቁሶች ድጋፍ አድርጓል።
የድጋፍ ቁሳቁሶቹ በዩኒቨርሲቲው ፕረዚደንት ፕሮፌሰር ታደሰ ደጀኔ በኩል የተበረከቱ ሲሆን በዋናነት ለኩሽና፣ ለመኝታ፣ ለምግብና እና ሌሎች አገልግሎቶች የሚውሉ ናቸው።
በፕሮፌሰር ታደሰ ደጀኔ የተመራው የዩኒቨርሲቲው ልኡክ ቡድን አባላት በማእከሉ አረጋውያኑ፣ ህፃናቱ እና አእምሮ ሕሙማኑ ያሉበት ሁኔታ እንዲሁም በማእክሉ እየተሰሩ ያሉ የተለያዩ ስራዎች ጎብኝተዋል።
በመጨረሻም የእንብካቤ ማእከሉ አስተዳዳሪ አባ ገብረመድህን ለዩኒቨርሲቲው ልኡክ ቡድኑ አባላት የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክት በማስተላለፍ በማእከሉ እየተከናወኑ ያሉ ዘርፈ ብዙ ስራዎች ዝርዝር ገለጻ እና ማብራሪያ ሰጥተዋል።
*****//*****
ራያ ዩኒቨርሲቲ ፤ ነሐሴ 06 ቀን 2017 ዓ.ም
ዕውቀት ለማኅበረሰባዊ ለውጥ!
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ
*****//*****











