‎የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም ይሰጣል

‎የኢ.ፌ.ዲ.ሪ ትምህርት ምዘና እና ፈተናዎች አገልግሎት ጽ/ቤት ይፋ ባደረገው መርሃ ግብር መሰረት የ2017 የትምህርት ዘመን የኢትዮጵያ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ (12ኛ ክፍል) ፈተና ከሰኔ23እስከሐምሌ8/2017 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል።

‎በመርሃ ግብሩ መሰረት ወደ ዩኒቨርሲቲያችን የተመደቡ በወረቀትየሚፈተኑየተፈጥሮሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ21 እስከ 22/2017 ዓ/ም እንዲሁም የማህበራዊሳይንስ ተፈታኞች ከሰኔ 29 እስከ 30/2017 ዓ/ም ይገባሉ።
‎እንደ አገልግሎት ጽ/ቤቱ ይፋዊ መርሃ ግብር፤ በበይነ መረብ የሚፈተኑ ተፈታኞች ከመኖሪያ ቤታቸው በየቀኑ እየተመላለሱ በተመደቡበት መፈተኛ ማዕከል የሚፈተኑ ሲሆን አንደኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ የበይነ መረብ ተፈታኞች ከሰኔ23-25/2017 ዓ.ም እንዲሁም የማህበራዊ ሳይንስ ከሐምሌ01-03/2017 ዓ.ም እንደሚፈተኑ ተመላክቷል።
‎ሁለተኛ ዙር የበይነመረብተፈጥሮሳይንስ ፈተና ሰኔ26፣27እና30/2017 ዓ.ም እንዲሁም የማህበራዊሳይንስ ፈተና ሐምሌ4፣7እና8/2017 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል።
‎የፈተናው ይዘት በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያተኮረ በመሆኑ እያንዳንዱ ተፈታኝ በትምህርት ቤቱ የተማረበትን የተማሪመጽሐፍ መሠረት አድርጎ ተገቢ የሆኑ አጋዥ መጽሐፍትን ለበለጠ እውቀትና መረዳት በመጠቀም እንዲዘጋጅ አገልግሎቱ ጥሪውን አስተላልፏል።
‎በዚህ አጋጣሚ ራያ ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር የተመደቡለትን የወረቀት እና የበይነ መረብ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች ተቀብሎ ለመፈተን አስፈላጊውን የቅድመ ዝግጅት ስራዎቹን አጠናቅቆ በመጠባበቅ ላይ ይገኛል።
‎በመጨረሻም በፈተና ወቅት ለፈተና ስርቆትና ኩረጃ የሚውሉ ማንኛውንም ቁሳቁሶች መጠቀም የተከለከለ ነው ተብሏል።
‎*****‎****‎****‎****//*****‎****‎****‎****‎****

ራያ ዩኒቨርሲቲ ፤ ግንቦት 02 ቀን 2017 ዓ.ም
‎ዕውቀት ለማህበሰባዊ ለውጥ
‎የህዝብ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈፃሚ ጽ/ቤት
‎*****‎****‎****‎****‎****//*****‎****‎****‎****‎****