ማኅበራዊ_ትስስራችን_ለአብሮነታችን! በሚል መሪ ቃል የጎንደር ቃል ኪዳን ቤተሰብ ሀገር አቀፍ የልምድ ልውውጥ መድረክ እየተካሄደ ይገኛል

‎ማኅበራዊ ትስስራችን ለአብሮነታችን!” በሚል መሪ ቃል የጎንደር ቃል ኪዳን ቤተሰብ ሀገር አቀፍ የልምድ ልውውጥ መድረክ ዛሬ ሐምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም በጎንደር ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት እየተካሄደ ይገኛል።
‎መድረኩ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ከሰላም ሚኒስቴር እና ከጎንደር ከተማ አስተዳደር ጋር በመተባበር ያዘጋጁት ሲሆን የራያ ዩኒቨርሲቲ ፕረዚደንት ፕሮፌሰር ታደሰ ደጀኔ እና የዩኒቨርሲቲው የሀገር ግንባታ ፎካል ፐርሰን ዶ/ር ገሰሰ ንጉስን ጨምሮሁሉንም የዩኒቨርሲቲ ፕረዚደንቶች እየተሳተፉ ይገኛሉ።
‎በመድረኩ መክፈቻ ሥነ ሥርዓት ላይ የጎንደር ዩኒቨርሲቲ ፕረዝደንት ዶ/ር አስራት አፀደወይን፣ የሰላም ሚኒስቴር ሚኒስትር አቶ መሐመድ እንድሪስ፣ በሰላም ሚኒስቴር የሰላም ግንባታ እና ብሄራዊ መግባባት ዘርፍ ሚኔስቴር ዴኤታ ዶ/ር ከይረዲን ተዘራ፣ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ከንቲባ አቶ ቻላቸው ዳኘው፣ የጎንደር ከተማ አስተዳደር ም/ከንቲባ ወ/ሮ ደብሬ የኃላ የእንኳን ደኅና መጣችሁ መልእክት እና ስለ ልምድ ልውውጡ ሀሳብ ሲሰጡ የቃልኪዳን ቤተሰብ ፋይዳ፣ ስለአብሮነት፣ ፍቅር እና ማኀበረሰብን በማስተሳሰር ረገድ ስላለው ጠቀሜታና ለሰላም ስላለው አስተዋፅኦ በዝርዝር ተናግረዋል።
‎ሀገር አቀፍ የልምድ ልውውጥ መድረኩ በተለያዩ መርሐ ግብሮች የሚቀጥል ይሆናል።
‎*****‎*****‎*****‎*****//*****‎*****‎****
ሀምሌ 14 ቀን 2017 ዓ.ም
‎ዕውቀት ለማኅበረሰባዊ ለውጥ!
‎የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ
‎*****‎*****‎*****‎*****//*****‎*****‎***