‎የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እና አዲሱን የፌደራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ለአካዳሚክ መካከለኛ አመራሮች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ

‎በራያ ዩኒቨርሲቲ ብቃት እና ሰው ሃብት አሥተዳደር ሥራ አሥፈጻሚ ጽ/ቤት አዘጋጅነት የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አዋጅ ቁጥር 1152/2011 እና አዲሱን የፌደራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 ለኮሌጅ ዲኖች፣ ዳይሬክተሮች፣ አስተባባሪዎች እና የትምህርት ክፍል ሀላፊዎች ግንቦት 08/ 2017 ዓ.ም በዩኒቨርሲቲው ሰኔት መሰብሰቢያ አዳራሽ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጥቷል።
‎የዩኒቨርሲቲው ብቃትና ሰው ሃብት አሥተዳደር ሥራ አሥፈጻሚ አቶ ካሕሳይ ፍቃዱ የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አዋጅ ቁጥር 1152/2011 ፣ የከፍተኛ ትምህርት ምልመላ፣ ቅጥር እና ልማት መመሪያ ሕዳር 01/ 2011 እንዲሁም አዲሱን የፌደራል መንግስት ሰራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 መሰረት በማድረግ የሰራተኞች የደረጃ ዕድገት እና ዝውውር መመሪዎች ዝርዝር ገለጻ አድርገዋል።
‎በዩኒቨርሲቲው የሰው ሃብት አሥተዳደር በድን መሪ አቶ ብርሃኑ ግርማይ በበኩላቸው አዲሱን የፌደራል መንግስት ሠራተኞች አዋጅ ቁጥር 1353/2017 መሰረት አድርገው የሥራ ሰዓትና ፍቃድ፣ የመንግሥት ሰራተኞች የግል መረጃ አያያዥ እና አደረጃጀት እና የመንግሥት ሠራተኞች ሥራ ውል ማቋረጥ እና ማራዘም የሚሉ አጀንዳዎች ሙያዊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
‎በመጨረሻም ከዲኖቹ፣ ዳይሬክተሮች እና ትምህርት ክፍል ሀላፊዎች ጋር በተደረገ ውይይት የተለያዩ ሀሳብ አስተያየት እና ጥያቄዎች ተነስተው በሚመለከታቸው አካላት ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቷል።
‎*****‎*****‎*****//‎*****‎*****‎**********
ራያ ዩኒቨርሲቲ ፤ ግንቦት 09/ 2017 ዓ.ም
‎ዕውቀት ለማኅበረሰባዊ ለውጥ!
‎የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ሥራ አስፈጻሚ ጽ/ቤት
‎*****‎*****‎*****‎*****//*****‎*****‎*****‎*****‎*****