‎በዩኒቨርሲቲው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐግብር ተካሄደ

‎በራያ ዩኒቨርሲቲ ቅጥር ግቢ ውስጥ ዛሬ ሀምሌ 22 ቀን 2017 ዓ.ም የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ ተከላ መርሐግብር ተካሄዷል::
‎የራያ ዩኒቨርሲቲ ማኅበረሰብ በየዓመቱ የሚካሄደውን ሀገር አቀፍ የአረንጓዴ አሻራ መርሃግብር ምክንያት በማድረግ የዩኒቨርሲቲው ፕረዚደንት ታደሰ ደጀኔ (ፕሮፈሰር)፣ የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕረዚደንት ዶ/ር ነጋ ዓፈራ፣ የአስተዳደር እና ልማት ምክትል ፕረዚደንት ዶ/ር ክብሮም ካሕሱን ጨምሮ በየደረጃው የሚገኙ የዩኒቨርሲቲው ማኅበረሰብ በዘንድሮውን የችግኝ ተከላ መርሐግብሩ ተሳትፈዋል።
‎በአየር ንብረት ለውጥ ምክንያት ለሚከሰቱ የተለያዩ የተፈጥሮ አደጋዎች በዘላቂነት ለመከላከል ውጤታማ የአካባቢ ጥበቃ ስራዎች ሊሰሩ እንደሚገባ የገለጹት የዩኒቨርሲቲው ፕረዚደንት ፕሮፌሰር ታደሰ ደጀኔ ዩኒቨርሲቲያንም ይህን ለመተግበር የራሱን ድርሻ እየተወጣ መሆኑን ተናግረዋል::
‎*****//*****
‎ራያ ዩኒቨርሲቲ ፤ ሀምሌ 22 ቀን 2017 ዓ.ም
‎ዕውቀት ለማኅበረሰባዊ ለውጥ!
‎የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ
‎*****//*****