ከሰኔ 23 እስከ ሀምሌ 08/ 2017ዓ.ም በራያ ዩኒቨርሲቲ በወረቀት እና በበይነመረብ (Online) የተሰጠ ሀገር አቀፍ የ2017 ዓ.ም የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ማጠናቀቂያ እና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና በሰላም እና በስኬት ተጠናቀቀ።
በተፈጥሮ ሳይንስ ዘርፍ በወረቀት የተሰጠ የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሰኔ 23 – 25/ 2017 ዓ.ም ሲሆን፤ በበይነ መረብ (Online) ደግሞ ከሰኔ 26 – 30/ 2017 ዓ.ም ተሰጥቷል።
የ12ኛ ክፍል የማኅበራዊ ሳይንስ ፈተና ተፈታኞች በበኩላቸው ከሀምሌ 01 – 03/ 2017 ዓ.ም በወረቀት፤ ከሀምሌ 04 – 08/ 2017 ዓ.ም በበይነ መረብ ፈተናቸውን ወስደዋል።
ፈተናውን በተሳካ መንገድ እንዲጠናቀቅ አስተዋጽኦ ላበረከቱት አካላት ዩኒቨርሲቲው የላቀ ምስጋናውን ለማቅረብ ይወዳል።
ተፈታኝ ተማሪዎችም ፈተናው ተጀምሮ እስኪጠናቀቅ ላሳዩት የላቀ ስነ- ምግባር እያመሰገነ መልካም ዕድል እንዲገጥማቸው ዩኒቨርሲቲያችን ምኞቱን ይገልጻል፡፡
*****//*****
ራያ ዩኒቨርሲቲ ፤ ሀምሌ 08 ቀን 2017 ዓ.ም
ዕውቀት ለማኅበረሰባዊ ለውጥ!
የህዝብና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ስራ አስፈፃሚ
*****//*****